Sunday, December 26, 2010

የገና ዛፍ ለኢትዮጵያውን ተገቢ ነውን?

እኛ ኢትዮጵያውያን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰውና የአባቶቻችንን ህሊና አንቅቶ በቀመሩልን የዘመን አቆጣጠራችን መሰረት የጌታችንን ልደት በዓል መታሰቢያ የበዓሉን ምስጢር ከቤተ ክርስቲያናችን በተረዳንው መልኩ ወቅቱን ጠብቀን በየዓመቱ እናከብራለን፡፡ አከባበሩም ምስጢሩን የጠበቀ ሃይማኖታዊ ባህል አለው፡፡ ይሁን እንጂ ዛሬ ዛሬ ሳናውቀው ተለመደንና በቤታችን፣ በስጦታችን፣በፌስቡክ ፕሮፋይላችን ሁሉ የምዕራባውያንን ባህል ወርሰን ‘የገና ዛፍን’ ለበዓሉ መግለጫ እንጠቀምበታለን፡፡ለምዕራባውያን የገና ዛፍ እራሱን የቻለ ለጌታችን ልደት ግን ያልተገባ ታሪክ አለው፡፡ እስቲ ‘የገና ዛፍ’ ከጌታችን ልደት ጋር ምን አገናኘው? መጠቀማችንስ አግባብ ነው ትላላቸሁ?ብንወያይ?

No comments:

Post a Comment